ፕሬዝዳንቱ በኒወርክ ክልላዊ መንግስት ዓቃቤ ህግ  በኩል በአንድ መዝገብ 34 ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ የክሱ ዋና መነሻ ምክንያት የንግድ የሂሳብ መዝገብ ላይ ሀሰተኛ ሰነድ አያይዘዋል የሚል ነው፡፡ ሀሰተኛ ሰነድ ያያዙት ደግሞ ለማጭበርበር እና ሌሌ ወንጀል ለመፈፀም ወይም ለመደበቅ ወይም ለማገዝ ሆን ብለው የፈፀሙት እንደሆን ይገልፃል፡፡ 34ቱም ክሶች አንድ ዓላማ ለማሳካት  በተለያየ ወቅት የተፈፀሙ ድርጊቶች ቢሆንም ለእያንዳንዱ ድርጊት ለብቻው ክስ ቀርቦበታል፡፡ ከሀገራችን የወንጀል ህግ እና ክስ አመሰራረት አንፃር እንዴት ያዩታል?

Leave a comment