በሰራተኛ ቅጥር ሂደት ስለሚፈፀም የኋላታሪክ ፍተሻ፣ አስፈላጊነት እና ሕጋዊነት

መግቢያ

በዚህ የውድድር ዘመን አሰሪዎች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ወይም ምርት በጥራት እና በፍጥነት ለደንበኞቻቸው ማቅረብ ይገባቸዋል። ከዚህም ባለፈ አንዳንድ ሙያዎች በባህሪያቸው በአደራና እምነት ላይ የተመሰረቱ (positions of trust) ስለሆነ ሰራተኛው ለዚህ የሥራ መደብ የተገባ መሆን ይገባዋል።  በመሆኑም አሰሪዎች መልካም ስማቸውን ጠብቀው የገበያ ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ በቴክኖሎጂ እና በሰለጠነ የሰው ሃይል ተቋማቸውን ያጠናክራሉ። ሆኖም ግን የሰው ሃይል ቅጥር በሚፈፅሙበት ወቅት ከግለሰብ የግል ባህሪ እና በዲጅታል ቴክኖሎች መሳሪያዎች ሀሰተኛ ሰነድ ለማዘጋጀት ከመቼው ጊዜ በላይ ለመለየት በሚያስቸግር መልኩ ረቂቅ፣ በቀላሉ የሚገኝና ተግባር ላይ የሚውል በመሆኑ የቅጥር መስፈርቱን የማያሟላ እና ለስራው ትክክለኛና ተገቢ ያልሆነው ስራተኛ እንዲቀጥሩ በማድረግ ከገበያ ተወዳዳሪነት የሚያስወጣ የስጋት ተጋላጭነታቸውን አሳድጎታል። 

በአደጉ ሃገራት ይህን ችግር ለመፍታት በቅጥር ሂደት ወቅት የሥራ ቅጥር አመልካቹን የኋላ ታሪክ ህግን በተከተለ መልኩ በሦስተኛ ወገን መርማሪዎች ወይም አሰሪዎቹ በራሳቸው በማጣራት ትክክለኛ የትምህርት ማስረጃ፣ የሥራ ልምድ፣   የስነ ልቦና እና የአካል ብቃት ያለውን በመቅጠር መልካም ስማቸውን እና የኢንዱስትሪ ሰላማቸውን በማረጋገጥ የገበያ ተወዳዳሪነታቸውን ያረጋግጣሉ። 

በሃገራችንም በቅጥር ወቅት የኋላ ታሪክን የመፈተሽ ተግባር ከላይ የተመለከቱትን የስጋት ተጋላጭነቶችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ በአግባቡ ምርመራ ሲደረግ አይስተዋልም። በመንግስት መስሪያ ቤት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሰራተኞችን የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ተግባር እየተከናወነ ይገኛል። የዚህ ፅሁፍ ፀሃፊ በተሳተፈበት የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ማጣራት ተግባር በሃሰት በተዘጋጀ የትምህርት ማስረጃ ወይም አግባብነት ባለው ባለስልጣን እውቅና ባልተሰጣቸው ኮሌጆች ተምረው የተቀጠሩ ሰራተኞች ሊገኙ ችለዋል።  በዚህም የመንግስት ሃብት ተገቢነት በሌላቸው ሰራተኞች ከመባከኑም ባለፈ ደረጃውን ያልጠበቀ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ በመስጠት የመልካም አስተዳደር እጦት እና ለብልሹ አሰራር መስፋፋት እንደ አንድ ገፊ ምክንያት ሊጠቀስ እንደሚችል ይታመናል። በማጣራት ሂደቱ ሰራተኞቹ የተማሩበት ኮሌጆች እና ዪንቨርስቲዎች የፍተሻውን ህጋዊነት ከግላዊነት መብት(Privacy right) ጥበቃ አኳያ  መረጃዎቹን ሊሰጡ የሚችሉት ተመራቂ የቀድሞ ተመሪዎቻቸው ፍቃዳቸውን የሰጡበት ህጋዊ ሰነድ ወይም የፍርድ ቤት ማዘዣ ካልቀረበ መረጃውን አሳልፈው እንደማይሰጡ ክልከላ ሲያደርጉ ተስተውለዋል። 

በመሆኑም በዚህ ፅሁፍ በቅጠር ወቅት የኋላ ታሪክ ፍተሻ አስፈላጊነት፣ በሃገራችን ተግባሩን የሚፈቅድ ወይም የሚከለክል ህግ ስለመኖሩ፣ የህግ ወሰን ወይም ቅድመ ሁኔታ ከኖረ ይህንኑ አክብሮ የኋላ ታሪክ ፍተሻ ስለሚደረግበት ሁኔታ አግባብነት ካላቸው የሃገራችን ህጎችን አንፃር እንመለከታለን። 

እመን ግን አረጋግጥ

በስራ ቅጥር ሂደት የሚፈፀም የኋላ ታሪክ ፍተሻ (background screening) (ከዚህ በኋላ “ፍተሻ” ወይም “ምርመራ” እየተባለ የሚገለፀው) አሰሪ የሥራ ውል ከመፈፀሙ በፊት የሥራ ውድድር መስፈርቱን አሟልቶ ለቅጥር ብቁ የሆነውን አመልካች ወይም እጩ ሰራተኛ የትምህርት የስራ ልምድ ከወንጀል ነፃ ማስረጃ እና ሌሎች አስፈላጊ ማስረጃዎችን ትክክለኝነት በራሱ ወይም በሶስተኛ ወገን የሚፈትሽበት አሰራር ነው። ከላይ በመግቢያው ላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው ከአንዳንድ ስራዎች ተፈጥሮ አስገዳጅነት፣ የሰራተኛው የግል ባህሪና ጤንነት እና ከዲጅታል ቴክኖሎጂ የኪሳራ ስጋትት አጋላጭነት አንፃር አሰሪዎች በመተማመን ላይ የተመሰረተ የሰራተኛ የቅጥር ሁኔታን ለማቆም ተገደዋል። 

ውቧ ቀስተ ደመና ያለ ካፊያ ዝናብ አትወጣም እንዲሉ የዲጅታል ቴክኖሎጂ በሚያስደምም ሁኔታ ለሰው ልጅ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታን ያስገኘ ቢሆንም በተቃራኒው ለእኩይ ተግባር መዋሉ አልቀረም። ለእኩይ ተግባር በመዋል ረገድ ሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ፣ የሥራ ልምድ እና የመልካም ስነ ምግባርና የሥራ አፈፃፀም የምስክር ወረቀቶችን ፍፁም ለመለየት በሚያስቸግር መልኩ (deepfake)  ለማዘጋጀት ጥቅም ላይ እያዋለ ይገኛል። ማህበራዊ ሚድያዎችም የሰራተኛን ምርታማነት በሚቀንስ ሁኔታ ጊዜን እና ትኩረትን ከስራ ላይ በመስረቅ በአሰሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ። ከግለሰብ ባህሪ የሚመነጭ የስራ ከባቢ  አምባጓሮን እና ምርታማነት የመቀነስ  ስጋትን ቀድሞ ለመከላከል የቀደመ የወንጀል ጥፋተኝነት እና የዕፅ ወይም የአልኮል ወይም የማህበራዊ ሚድያ ሱሰኝነት በቅጥር ወቅት እንዲያጣሩ ተገደዋል። ለዚህም ነው፣ የግል የምርመራ ተቋማት የዘመኑ ቴክኖሎጂ ረቂቅነት እና በቀላሉ ተደርሽ ሆኖ ለእኩይ ተግባር እየዋለ መሆኑን ተረድተው ለደንበኞቻቸው “እመን ግን አረጋግጥ” የሚል ምክር በመለገስ ቅድመ መከላከል ላይ ያተኮረ የሰራተኛ ቅጥር ፓሊሲ እንዲከተሉ የሚያደርጉት። ከዚህ አንፃር በሌሎች ሃገሮች አሰሪዎች የሰራተኛ ቅጥር ውል ከመፈፀማቸው በፊት የአመልካቹን የኋላ ታሪክ በተመለከተ ትኩረት አድርገው የሚመረምሩዋቸውን ጉዳዩች እና አስፈላጊነት ለማየት እንሞክራለን። 

  • የትምህርት ማስረጃ 

በመሆኑም በሙያው ሳይማር ወይም ሳይሰለጥን በተለያየ መልኩ የሃሰት የትምህርት ማስረጃ በማዘጋጀት መንግስትና በግል ተቋማት በመቀጠር ያልተገባ ጥቅም በማግኘት ሃብት ከማባከናቸው ባለፈ ከሙያው ሊገኝ የሚገባውን ደረጃውን የጠበቀ ጥራት ያለው አገልግሎት ወይም ምርት ባለ መስጠት እና መልካም ስምና ዝና እንዲያጡ ያደርጋል። ከዚህም በተጨማሪ ቀጣሪ ተቋማቱ ተገቢውን የትምህርት ማስረጃ ባልያዘ ሰራተኛ ምርትና አገልግሎት በመስጠታቸው የህግ ተጠያቂነት ሊያስከትልባቸው ይችላል።  

የትምህርት ማስረጃ የአንድን ተቀጣሪ በሙያው መስክ ያለውን ዕውቀት እና ክህሎት የሚመዘንበትና ተገቢነቱ የሚረጋገጥበት ነው። ዘመኑ ከደረሰበት የዲጅታል ቴክኖሎጅ እድገት አንፃር የትምህርት እና ሌሎች ማስረጃዎች ፍፁም በተመሳሰለ መልኩ ሰዉ ሰራሽ የአስተውሎት ቴክኖሎጁን ( AI generated deepfake text and images) በመጠቀም በቀላሉ ላሊዘጋጁ ይችላሉ። እንዲሁም የትምህርት ጥራትና ብቃት ማረጋገጫ ተቋም ፍቃድ ባልሰጣቸው የትምህርት ተቋማት ተምረው ወይም አስፈላጊውን የምዘና ፈተና ሳያልፉ ሃሰተኛ ማስረጃ ይዘው ለቅጥር የመቅረብ ሁኔታ ይታያል። 

በመሆኑም የተቀጣሪዎችን የትምህርት ማስረጃ በማረጋገጥ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ቀድሞ ማስወገድ ይገባል። 

  • የሥራ ልምድ 

ብዙውን ጊዜ ከመቀጠር ፍላጎትና ጉጉት የተነሳ ስራ ቅጥር አመልካቾች የቀደመ የሥራ ልምድን በተመለከተ የተጋነነ ወይም የተሳሳተ መረጃ እንደሚሰጡ ጥናቶች ያመለክታሉ። አሰሪዎቹም ይህን ስለሚያውቁ ትክክለኛ የስራ ልምድ ያለው ስለመሆኑ ማረጋገጥ እንዳለባቸው ያምናሉ። ይህ የማረጋገጥ ተግባር የሰራተኛውን ልምድ ብቻ ሳይሆን ስለ ታማኝነቱ፣ ስብዕናውን እና ተረጋግቶ ለረዥም ጊዜ ከአሰሪው ጋር የመዝለቅ ባህሪውን ለማወቅ ይጠቅማል። በመሆኑም ተቀጣሪው ያቀረበው የስራ ልምድ ከተረጋገጠው ጋር ልዩነት ወይም አለመጣጣም ካለ ስለዚሁ ጉዳይ ለመጠየቅ እድል ይሰጣል፣ ወደፊት ሊኖራቸው የሚችለውን መተማመን ላይ የተመሰረተ ግንኙነት አስቀድሞ በማወቅ መረጃ ላይ የተመሰረት መሰረተ የቅጥር ውሳኔ ለማሳለፍ ይረዳል።  የስራ ልምድን ማረጋገጥ አመልካቹ ስራ የጀመረበትን እና ያቆመበትን ቀን፣ የስራ ተግባርና ሃላፊነት፣ ደሞዝና ጥቅማጥቅም፣ እና ሥራውን ያቋረጠበትን ወይም ለመልቀቅ ያቀረበውን ምክንያት ለማወቅ ያስችላል። 

  • የቀደመ ወንጀል ጥፋተኝነት ታሪክ

የአንድን ሰው ግለ ታሪክ ለማወቅ ስንነሳ መጀመሪያ ወደ አይምሮችን የሚመጣው የቀደመ የወንጀል ጥፋተኝነት እንዳለው ማጣራት ነው። የወንጀል ጥፋተኝነት ታሪክ ስለ ሰውየው ባህሪ ብዙ ነገር እንድንረዳ ያግዘናል። ይህም ተቀጣሪው ደንበኞች ላይ ስጋት ይፈጥራል ወይም  ምቹ ያልሆነ የስራ ከባቢ ይፈጥራል ወይስ አይፈጥርም የሚለውን ለመወሰን፣ ወንጀሉ ከስራው ባህሪ እና ከሙያው ጋር የተያያዘ መሆን አለመሆኑን ለማወቅ ለአሰሪው እድል ይሰጠዋል። ከዚህም በተጨማሪ በተለይም እምነት ላይ የተመሰረቱ የሥራ መደቦች(Trust positions) በትክክለኛና ተገቢነት ባላቸው ሰራተኞች እንዲያዙ እድል ይሰጣል። መምህራን፣ የሂሳብ ባለሙያዎች፣ ከፍተኛ የአስተዳደር ቦታዎች፣ የመንግስት ስራተኛ ወዘተረፈ በአደራ እና በእምነት የሥራ ግንኙነት ላይ የሚመሰረቱ የስራዎች ናቸው።  በመሆኑም እጩ ሰራተኛው የቀደመ የወንጀል ጥፋተኝነት ማረጋገጥ ተገቢ ይሆናል። በፌደራል እና ክልል ፓሊስ ተቋማት የወንጀል ሪከርድ ማጣራት ያስፈልጋል። 

  • ምስክርነትን ማረጋገጥ (Reference Check)

አንድ ዕቃ ከመግዛታችን በፊት ከዚህ ቀደም ገዝተው የተጠቀሙትን ስለጥንካሬው፣ ምቾቱና ጥራቱ እንጠይቃለን። በቅጥር ወቅትም አሰሪው ስለሰራተኛው ባህሪ፣ የስራ ትጋት፣ በቡድን የመስራት ብቃት፣ ለሙያው አበርክቶቱ፣ ስነ ምግባርና ሌሎች ጉዳዮች ምስክርነት ከሰጠው ባለሙያ ወይም ሃላፊ የማረጋጥ ይገባል። ይህ የማረጋገጥ ተግባር ከትምህርትና ከስራ ልምድ ይለያል። የምስክርነት ማረጋገጫ ትኩረት የሚያደርገው የሰራተኛውን የስራ አፈፃፀም እና አመለካከቱን ለመለየት ነው። ከስራ ቅጥር ማመልከቻው ከተመለከተው ምስክርነት ባለፈ ከቀድሞ ስራ ባልደረቦቹና ከሌሎች ሃላፊዎች ሊወሰድ ይችላል። 

  • የአልኮል ምርመራ Drug Screening

አካላዊ እና አይሞሮአዊ ጤንነቱ የተጠበቀ ሰራተኛ ለማንኛውም የስራ ዓይነት እና ሁኔታ አስፈላጊ ነው። ምርታማነት እና የአገርልግሎት ጥራት እንደሚጨምር እሙን ነው። ይህ ጤነኝነት ከሚረጋገጥባቸው መንገዶች አንዱ የዕፅ እና የአልኮል ምርመራ ነው። የተቀጣሪው ደም ውስጥ አደገኛ ዕፅ ወይም አልኮል ስለመኖሩ ማረጋገጫ ይሰጣል። ይህም ከሱስ በሚመነጭ የስራ አፈፃፀም ብቃት ማነስን፣ ከሰራተኛ ወይም ከደንበኛ ጋር የሚደረግ አምባጓሮን እና ጉዳትን ለመስቀረት ይረዳል። በተለይም የሥራ ባህሪው ይህን ቅድመ ሁኔታ እንዲያሟላ ሊጠይቅ ይችላል።  በአየር መንገድ እና በሹፍርና ቅጥር በአስገዳጅ ሁኔታ የአልኮል እና እፅ ምርመራ ሊደረግ ይገባል። 

በሃገራችን የኋላ ታሪክ ፍተሻ ሕጋዊነት 

ከሰራተኛ ቅጥር ጋር በተያያዘ አግባብነት ያላቸው የሃገራችን ህጎቸች የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011፣ የፌደራልና የክልል የመንግስት ሰራተኞች አዋጆች እና በልዩ ሁኔታ የራሳቸውን ሰራተኞች እንዲያስተዳድሩ ስልጣን የተሰጣቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ደንቦች ናቸው፡፡

የግል ድርጅቶችን በተመለከተ አሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ተፈፃሚነት ያለው ሲሆን የስራ ቅጥር በሚፈፀምበት ወቅት አሰሪው የስራ ቅጥር አመልካችን የኋላ ታሪክ ስለሚያጣራበት ሁኔታ አልደነገም። ሆኖም ግን ህግ አውጭው አዋጁን ለማውጣት ያስፈለገበትን ዓላማ ከኋላ ታሪክ ፍተሻ አስፈላጊነት ጋር ካመሳከርነው ተገቢነቱን እንረዳለን። አዋጁ መግቢያው ላይ ካስቀመጣቸው ዓላማዎች መካከል አሠሪና ሠራተኛ የጋራ ራዕይ ኖሯቸው የሥራ ግንኙነቶቻቸውን መሠረታዊ በሆኑና በህግ በተደነገጉ መብቶችና ግዴታዎች ላይ በመመስረት አስተማማኝ የኢንዱስትሪ ሰላም፤ የዘላቂ ምርታማነት እና የገበያ ተወዳዳሪነት አቅም በመፍጠር ሀገራችን ለተያያዘችው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የማስመዝገብ ብሔራዊ ግብ በትብብርና በጋራ እንዲሰሩ ማድረግ ሊያሳካው የሚፈልገው አንዱ ዓላማ እንደሆነ ይገልፃል። በመሆኑም አሰሪው የሰራ ቅጥር በሚፈፅምበት ወቅት የኌላ ታሪክ ፍተሻ ማከናውኑ በዋናነት ያልተገባ ሰራተኛ ቀጥሮ የኢንዱስትሪ ሰላሙን፣ ምርታማነትን እና የገበያ ተወዳዳሪነቱን እንዳያጣ አስቀድሞ ለመከላከል ስለሆነ የአዋጁን አላማ ያሳካል። በተጨማሪም ምርመራው የሚከናወነው የስራ አመልካቹ የሥራ መደቡ ላይ ለመቀጠር አስፈላጊ መስፈርቶቹን ስላማሟላቱ የሚያስረዱ የትምህርት፣ የስራ ልምድ እና ሌሎች ማስረጃዎችን በፍቃዱ ያቀረባቸውን መሰረት በማድረግ ስለሆነ በሁሉቱ መካከል ወደፊት ስለሚኖራቸው መተማመን የሚረገጥበት የመጀመሪያው አጋጣሚ በመሆኑ ሊበረታታ አመላካቹ የተሳሳተ መረጃ ካቀረበ ከቅጥሩ በፊት እምነት ሊጣልበት የማይገባ ስለመሆኑ ከወዲሁ ማረጋገጥ ያስችለዋል ። 

የፌደራል የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/201 የሰራተኛ ቅጥር በሚፈፀምበት ወቅት በምልምላና መረጣ ሂደት አመልካቹ ሊያሟላ ስለሚገባው ቅድመ ሁኔታ ከመደንገግ ውጭ ስለ ኋላ ታሪክ ፍተሻ የሚለው ነገር የለም። ከአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ የሚለየው በመርህ ደረጃ በአመልካቾች መካከል በብሄረሰብ፣ በፆታ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት፣ በአካል ጉዳት፣ በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ወይም በሌላም ሁኔታ በሥራ ፈላጊዎችም መካከል ልዩነት ማድረግ የሚከለከል ቢሆንም የመንግስት ሰራተኛ ለመሆን ብቁ የማያደርጉ ሁኔታዎችን በግልፅ አስቀምጧል፡፡ እነዚህም ቅጣቱ ከተፈጸመ፣ በይርጋ ከታገደ ወይም በይቅርታ ከተሠረዘ በኋላ አምስት ዓመት ያለፈው ካልሆነ በስተቀር የሙስና፣ የእምነት ማጉደል፣ የስርቆት፣ የማጭበርበር ወይም የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈጽሞ ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት የተፈረደበት ማንኛውም ሰው፣ ብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ የሌለው ሰው፤ በዲስፕሊን ጉድለት ምክንያት ከሥራ የተሰናበተ ሰው ከሥራ ከተሰናበተበት ጊዜ ጀምሮ አምስት ዓመት ከመሙላቱ በፊት በመንግሥት ሠራተኛነት ሊቀጠር አይችልም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ማንኛውም አመልካች በመንግሥት ሥራ ተቀጥሮ ለማገልገል ብቁ መሆኑን ለማረጋገጥ ከኤች.አይ.ቪ./ኤድስ ምርመራ በስተቀር የጤንነት ማረጋገጫ የሕክምና ምርመራ እና ለቅጥር የማያበቁ ተብለው ከተጠቀሱት ወንጀሎች ነጻ መሆኑን የሚያረጋግጥ ከፖሊስ የተሰጠ ማስረጃ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡(አንቀፅ 13 እና 14 ይመለከቷል) 

የጤና ማረጋገጫ የሕክምና ምርመራ የዕፅ እና የአልኮል ሱሰኝነትን ለማጣራት የሚደረግ ምርመራን ያካትታል ? የሚለው ጥያቄ አከራካሪ በመሆኑ ምላሽ ይሻል። አዋጁ እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች በምልመላና መረጣ ወቅት ያስቀመጠው የመንግስት ሥራ በፍፁም ታማኝነት እና የአገልግሎት ጥራት ደረጃ መሰራት እንዳለበት ለማመልከት ነው። በመሆኑም ቅድመ ሁኔታዎቹ በሥራ አመልካቹ መሟላታቸውን በአግባቡ የኋላ ታሪኩን በመፈተሽ የቅጥር ውል መፈፀም ይበልጥ የአዋጁን አላማ ያሳካል። 

የግላዊነት መብት ጥበቃ (Privacy protection)

ከግላዊነት መብት ጥበቃ አንፃር የሚነሳው ጥያቄ የቀድሞ አሰሪዎች እና ከፍተተኛ ትምህርት ተቋማት እንደቅደም ተከተሉ የቀድሞ ሰራተኛቸውን እና ተማሪዎቻቸውን መረጃ አሳልፈው ለመስጠት የግላዊነት መብት ጥበቃ ሕጎች ይፈቅዱላቸዋል ወይ ? የሚል ነው፡፡

በቅጥር ወቅት የሚፈፀም የኋላ ታሪክ ፍተሻ የህገ መንግስት ጥበቃ ካለው የግላዊነት መብት (privacy right) ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ህግን ባከበረ መልኩ መፈፀም ይገባዋል። የትምህርት ማስረጃ፣ የጤና ሁኔታ ምርመራ፣ የስራ ልምድ እና ሌሎች ሁኔታዎች በግላዊነት መብት ጥበቃ የሚደረግላቸው ናቸው። በመሆኑም ህግን መሰረት በማድረግ ወይም በግለሰቡ ፍቃድ ካልሆነ በስተቀር በማናቸውም ሁኔታ አይደፈሩም ።(ህገ-መንግስት አንቀፅ 26 እና ፍትህ ብሄር ህግ ስለ ሰዎች መብት የተመለከቱትን ድንጋጌዎች ይመለከቷል)።  በመሆኑም በሥራ ቅጥር ወቅት አመልካቹ ያቀረባቸውን ማስረጃዎች ትክክለኝነት ከሶስተኛ ወገኖች ቀርቦ ለማጣራት ፍቃዱን መስጠት ይገባዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ፀሃፊው የደቡብ ክልል አቃቤ ህግ ሆኖ በሚሰራበት ወቅት ክልል አቀፍ መንግስት ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ የማጣራት ግብረ ሃይል አባል ሆኖ የተሳተፈ ሲሆን ሰራተኞች በተማሩባቸው ዩንቨርስቲዎችና ኮሌጆች በመሄድ የማጣራት ተግባር በሚፈፅምበት ወቅት የግላዊነት መብት ጥበቃን መሰረት በማድረግ አንዳንድ ዩንቨርስቲዎች መረጃ አሳልፈው ለመስጠት ፍቃደኛ ሳይሆኑ እንደቀረ ያስታውሳል። የዩንቨርስቲዎቹ የመከራከሪያ ሃሳብ ከቀድሞ ተመራቂዎቻችን ይህን የማጣራት ተግባር እንድትፈፅሙ ፍቃዳቸውን የገለፁበት ህጋዊ ውክልና ወይም በፍርድ ቤት የምርመራ ማዘዣ ሳትይዙ መረጃውን እንድንሰጥ አንገደድም፣ አሳልፈን ብንሰጥ ተያቂነት ያመጠብናል የሚል ነበር። በወቅቱ ይህ የመከራከሪያ ሃሳብ ትክክል እና ህጋዊ መሆኑን በመረዳት የሰራተኞቹን ውክልና ለመቀበል እጅግ አስቸጋሪ ሆኖ በመገኘቱ የፍርድ ቤት የምርመራት ትዕዛዝ ማዘዣ በማውጣት ችግሩን ልንፈታ ችለናል። 

በመሆኑም የትምህርት ማስረጃ፣ የጤና፣ የስራ ልምድ ፣ የመልካም ምግባርና የሥራ አፈፃፀም ምስክርነት እና ከወንጀል ነፃ መረጃ ከግላዊነት መብት ጋር እጅግ የተቆራኘ እና ሊከበር የሚገባ በመሆኑ መረጃው ከሚገኝበት ከሶስተኛ ወገን በቅርብ  ለማጣራት የሥራ አመልካቹን ፍቃድ መቀበል አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ ነው። የማጣራት ተግባሩ በአሰሪው ወይም አሰሪው በሚቀጥረው ይህንኑ ለመፈፀም ህጋዊ ፈቃድ ያለው አካል የአመልካቹን ፍቃድ በግልፅ መቀበል ይገባዋል። ከዚህ ጋር አግባብነት ያለው የፍቃድ አሰጣጥ ሂደት በፍትሃብሄር ህጋችን አንቀፅ 2032 መሰረት ውስን ውክልና በመስጠት ይሆናል። ይህ ውስን የውክልና ስልጣን ወካዩ መብቱ እንዳይጎዳ ስልጣኑን በማገደብ ለሚፈለገው አላማ ብቻ እንዲውል በመፍቀድ መብቱን እንዲጠብቅ ያስችለዋል። ከዚህም በተጨማሪ ይህ ውክልና በሰነድ አረጋገጭ ፊት ቀርቦ መረጋገጥና መመዝገብ አለበት። 

የግል ምርመራ ተቋማት አስፈላጊነት 

ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው የምርመራ ተግባሩ በአሰሪው ወይም ይህንኑ ተግባር ለመፈፀም ህጋዊ የሥራ ፈቃድ ባለው አካል መሆን ይገባዋል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ሊነሳ የሚገባው ጉዳይ በሃገራችን የግል የምርመራ ተቋማት ስለሌሉ ተግባሩ የሚፈፀመው በአሰሪው ብቻ እንዲሆን ያስገድዳል። በሌሎች ሃገራት የኋላ ታሪክ የመመርመር ተግባር ፍቃድ ባላቸው የምርመራ ባለሙያዎች እውቀትና ክህሎት በመታገዝ የሚፈፀም ሲሆን ጥራት ያላው መረጃ እንዲያገኙ ያስችላል። በመሆኑም አሰሪዎች ትኩረታቸውን እና ጊዜያቸውን በተቋማቸው ስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ በማዋል ከቅጥር ጋር ተያይዞ ያለውን የኋላ ታሪክ ማጣራት ተግባር ለግል የምርመራ(Private investigation) ተቋማት ይሰጣሉ። የውጭ ሃገር ኢንቨስተሮች ወደ ሃገራችን ሲገቡ የሰራተኛ ቅጥር ሁኔታን በተመለከተ የተቋማቸው ባህል የሆነውን እና በሌሎች ሃገሮች የለመዱትን የኋላ ታሪክ ምርመራ በግል የምርመራ ተቋማት እንዲፈፅምላቸው ስለሚፈልጉ በዚህ ረገድ ክፍተት እንደሚገጥመን ማወቅ ይገባል። በመሆኑም የህግ እና የአስተዳድር ክፍተቶችን በማስተካከል የግል የምርመራ ተቋማት ወደ ሥራ የሚገቡበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይገባል። 

ማጠቃለያ 

የግል የንግድ ተቋማት አስተማማኝ የኢንዱስትሪ ሰላም፣ ዘላቂ ምርታማነት እና የገበያ ተወዳዳሪነት አቅም በመፍጠር ምርትና አገልግሎታቸውን በማቅረብ የንግድ ትርፍ የማግኘት ዋና አላማ አላቸው። የመንግስት መስሪያ ቤቶችም እንዲሁ በሕዝብ የተጣለባቸውን አደራ በማክበር ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት መልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነት እንዲከበር ያደርጋሉ። ሁለቱም አሰሪዎች ይህን አላማቸውን ለማሳካት የሰው ሃብት አስተዳደራቸው ውጤታማ መሆን ይገባዋል። ሆኖም ግን ከአንዳንድ የሥራ ሙያዎች ተፈጥሮ፣ ከግለሰብ ባህሪ እና ከዲጅታል ቴክኖሎጂ በሚመነጭ የችግር ተጋላጭነት ምክንያት ውጤታማ የሰው ሃብት አስተዳደር እንዳይኖር በማድረግ የሚፈልጉትን ዓላም እንዳያሳኩ እያደረገ ይገኛል። ይህን ችግር ለመፍታት ሃገራት በስራ ቅጥር ወቅት የስራ አመልካችን የኋላ ታሪክ አግባብ ያላቸውን ህጎች አክብሮ በመመርመር ተገቢ የሆነውን ብቻ በመቅጠር  ላይ የተመሰረተ የሰው ሃብት አስተዳደር ሥርዓት ዘርግተዋል። በሃገራችን በግል ዘርፉ ብዙም ባይስተዋልም የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰራተኞቻቸውን የትምህርት ማስረጃ በማጣራት የሰው ሃብት አስተዳደራቸውን የማስተካከል ተግባር እየፈፀሙ ይገኛል። የዚህን ተግባር ህጋዊነት አግባብነት ካላቸው ህጎች አንፃር ስንመረምር በህግ በመፍቀድ ወይም በመከልከል ረገድ የተደነገገ ባይሆንም ህጎቹ ሊያሳካኩት ከሚፈልጉት ዓላማ አንፃር በቅጥር ወቅት የሥራ አመልካችን የኋላ ታሪክ ማጣራት ተገቢነት እንዳለው መረዳት እንችላለን። ሆኖም ግን የምርመራ ተግባሩ ከግላዊ መብት ጥበቃ አንፃር በስራ አመልካቹ ሙሉ ፍቃድ ላይ ተመስርቶ መፈፀም ይገባዋል። አሰሪው የምርመራ ተግባሩን መፈፀም የሚችል ቢሆንም ይበልጥ የምርመራ ሙያ እውቀት፣ ክህሎትና ዘዴዎች ባለቤት በሆነ የምርመራ ተቋማት የሚፈፀም ቢሆንም በኛ ሃገር የተለመደ አይደለም። ሃገራችን ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ የምታደርገውን ጉዞ የሚያግዝ በመሆኑ የህግና አስተዳደራዊ ክፍተቶችን በማስተካከል የግል የምረማራ ተቋማት ወደ ሥራ የሚገቡበት ሁኔታ ማመቻቸት ይገባል። 

በኢትዮጵያ መንግስትና በሕወሃት መካከል የተደረከ የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ሙሉ ሰነድ

“የህግ የበላይነት ሲባል…..”

በኃይለማርያም ይርጋ
መግቢያ

የኛ ሰው ፀብ የለሽ በዳቦ የሆነ አምባጓሮ ሲገጥመው፣ ንብረቱ ሲደፈር፣ ቃል አባይ በሆነ ሰው ሲከዳ፣ በመንግስት አካላት ሆነ በግለሰብ መብትና ጥቅሙ ያለ አግባብ ሲገፈፍ ፍትህ በ’ጄ ብሎ መብቱን በሃይል ከማስከበር ይልቅ በህግ አምላክ& ብሎ እማኝ ቆጥሮ ጉዳዩን ወደ ባህላዊ ፍርድ ሰጪ ወይም ህግ አስከባሪ አካል ወይም መደበኛ ፍርድ ቤት ይዞ በመሄድ መብቱን የማስከበር አኩሪ ባህል አለው። ይህ ባህል የሁሉም የክልላችን ህዝቦች መገለጫ ነው። ከመደበኛው የፍትህ አስተዳደር በተጨማሪ የሲዳማው አቦ ወንሾ ፣ የጉራጌው ጆካ፣ የየሙ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት ወ.ዘ.ተ በክልላችን ከሚገኙ ርዕትእንና ህገ ልቦናን መሰረት ያደረጉ ባህላዊ የፍትህ ሥርዓቶች ናቸው። ይህ የሚያሳየው የሃገራችን ዜጎች ምን ያህል ለህግ ተገዥ መሆናቸውን ነው። ሆኖም ግን በሃገራችን የተፈጠረውን የለውጥ ሂደት ተከትሎ አንዳንድ የሃገራችን ክፍሎች ውስጥ ሥርዓት አልበኝነት በመንገሱ መሰረታዊ የግለሰብና የቡድን መብቶች ሲጣሱ ይስተዋላል። በመሆኑም ፓለቲከኞች፣ ኢንቨስተሮች፣ ነጋዴዎች፣ ሙሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ተማሪዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች መንግስት &የህግ የበላይነት ያስከብር በማለት በልዩ ልዩ መገናኛ ብዙሃን መልእክት ሲያስተላልፉ ማየት የተለመደ ሆኗል። በተጨማሪም የመንግስት ባለስልጣናት በአንድ ጉዳይ ላይ ያሳለፉት ውሳኔ የህግ የበላይነትን ለማስከበር እንደሆን ሲገልፁ በሌላ በኩል ደግሞ ተፎካካሪዎችና ሊሂቃን ውሳኔው የህግ የበላይነትን የተቃረነ መሆኑን በመግለፅ ተፈፃሚነቱን ሲቃወሙ ይስተዋላል። ለመሆኑ ይህ አሳሳቢ የሆነው የህግ የበላይነት፤ ምን ማለት ነው? መስፈርቶቹስ? ጠቀሜታዎቹስ የሚሉትን ጉዳዮች ከሃገራችን ህጎች እና አለም አቀፍ ተቀባይነት ካላቸው መለኪያዎች አንፃር እናያለን። አንባቢ ልብ ሊለው የሚገባው ጉዳይ የህግ የበላይነት በፅንስ ሃሳብ ደረጃ በህግ ሙሁራን ዘንድ ክርክር እየተደረገበት ያለ ያልተቋጨና ብዙ መፅሃፍች የተፃፈበት ግዙፍ ሃሳብ መሆኑን ነው። በመሆኑም በዚህ የግንዛቤ መስጫ ፅሁፍ የፅንሰ ሃሳቡን አንኳር ነጥቦች ብቻ የምንመለከት ይሆናል።

የሕግ የበላይነት ትርጉም

በኢፌድሪ ሕገመንግስት መግቢያ ላይ “ በሃገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዲሞክራሲ እንዲሰፍን፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገታችን እንዲፋጠን…..በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ አንድ ፓለቲካል ኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት..” በሚል የሕግ የበላይነት ለሃገራችን ግንባታ ወሳኝ እንደሆነ ይገልፃል፡፡ ሆኖም ግን የሕግ የበላይነት የሚለው ቃል በህገ መንግስቱም ሆነ በሌሎች አለም አቀፍ የቃል ኪዳን ሰነዶች ቢጠቀስም ስምምነት ላይ የተደረሰበት አንዳች ትርጉም ሲሰጠው አይስተዋልም፡፡ ከመዝገበ ቃላት ትርጉም ይልቅ የተሟላ ግንዛቤ ይረዳን ዘንድ ዊሊያም ጋርድነር የተባለ የሕግ ሙሁር “THE HISTORY AND ELEMENTS OF THE RULE OF LAW” በተሰኘው መፅሀፍ ላይ ያስቀመጠውን ትርጉም እና የተባበሩት መንግስታት ድርግጅት ዋና ዳይሬክተር በ2014 እኤአ ለፀጥታው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፓርት ላይ ለህግ የባላይነት የተሰጠውን ትርጉም እናያለን፡፡

ዊሊያም የህግ በላይነትን አጭር እና ግልፅ በሆነ አገላለፅ እንደሚከተለው ይተረጉመዋል ፤

“የሕግ የበላይነት ማለት የመንግስት አካላት፣ ባለስልጣናት(ሰራተኛውን ጭምሮ) እና ዜጎች በሕግ ጥላ ስር ሲወሰኑና ሲያክብሩ ነው “ የሚል ነው፡፡

በአንድ ማህበረሰብ የመንግስት ባለስልጣናትና ዜጎች የእለት- ተለት ስራቸውን የሚፈፅሙት በህግ ጥላ ስር ሆነው ህግን በማክበር ከሆነ በህግ የበላይነት የሚመራ ማህበረሰብ ይባላል፡፡ በዚህ ትርጉም ውስጥ የተገለፀው ህግ ለውጥን ሊያስተናግድ በሚችል መልኩ በጠቅላላ አገላለፅ የተረቀቀና በቀላሉ የሚረዱት፣ ተደራሽ የሆነ፣ ሊፈፀም የሚችል፣ ሁሉም በህግ ፊት እኩል የሆነበት እንዲሁም ህጉ በማይከበርበት ወቅት የማስፈፀሚያ ስርዓትና ተቋማት ሊኖረው ይገባል ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ካልተሟሉ የሕግ የበላይነት ሊኖር አይችልም ይላል ዊሊያም፡፡ ለምሳሌ ህጉን የማስፈፀሚያ ስርዓት እና ተቋማት ከሌሉ ወይም ስራቸውን በአግባቡ ካልተወጡ የሕግ የበላይነት እንደሌለ ይቆጠራል፤ ባለስልጣኑም ሆነ ዜጋው ልጓም እንደሌለው ፈረስ እንዳሻው ይፈነጫል ማለት ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዊሊያም ከሰጠው ትርጉም በሰፋ መልኩ እንደሚከተለው ይተረጉመዋል:-

“ የሕግ የበላይነት የአስተዳደር መርህ ሲሆን ሁሉም ሰው፣ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት በግልፅ በፀደቀ፣ ያለአድሎ በእኩል በሚፈፀም፣ በገለልተኛ ፍርድ ቤት በሚተረጎም እና ከአለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች የቃል ኪዳን ሰነዶች ጋር በተጣጣመ ህግ ተጠያቂ መሆንን የሚያመለክት ሲሆን ተጠያቂነትን፣ ርትዕን፣ ተገማችነትን፣ የስልጣን ክፍፍልን፣ በውሳኔ ሰጪነት ተሳታፊነትን፣ የዘፈቀደ አሰራርን ለማስወገድ እና የህግና የሥነ ስርዓት ግልፀኝነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ሂደትና ጥረት ይጨምራል” በማለት ይተረጉመዋል፡፡

ፅንሰ ሃሳቡን የሚያጠኑ የሕግ ሊሂቃኖች ከላይ ከተመለከቱት ትርጉሞች አንፃር እይታቸው በሁለት የሚከፈል ሲሆን ሕጋዊነትን መሰረት ያደረገ ዝቀተኛው (formal or procedural conception) እይታ እና መሰረታዊ ፍሬ ነገሮችን ያካተተ (substantive conception) የህግ የበላይነት በሚል ይከፈላል፡፡ ህጋዊነትን መሰረት ያደረገው ዝቅተኛው የሕግ የበላይነት እይታ ዊሊያም ከሰጠው ትርጉም ጋር ተመሳሳይ ሲሆን ህግ መሰረታዊ የአስተዳደር መሳሪያ ሲሆን አግባብ ባለው ባለስልጣን ይመነጫል፣ ግልፅ፣ ተደራሽ፣ ተገማች፣ የረጋ እና ወደ ፊት የሚፈፀም መሆን እንደሚገባው ይገልፃሉ፡፡ መሰረታዊ ፍሬ ነገሮችን መሰረት ያደረገው የህግ የበላይነት እይታ አንድ ህግ ቅቡል ለመሆን ከሥነ ስርዓታዊ መስፈርቶች በተጨማሪ የሞራል ቅቡልነት ያለው፣ ርትዕንና ሰብዓዊ መብቶችን እና ሌሎች ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎችን ያከበረ መሆን ይገባዋል የሚል ነው፡፡ የኢፌድሪ ህገ መንግስት በአንቀፅ 9 ንዑስ አንቀጽ ማንኛውም ህግ፣ ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከዚህ ህገ መንግስት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት እንደሌለው በመደንገግ በመንግስት ስልጣን ላይ ገደብ አስቀምጧል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ የምንረዳው መንግስት ምንም እንኳ ህጋዊ መስፈርቶችን ያሟላ ህግ ቢያወጣም ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎችን ካላከበረ ህጉ ተፈፃሚነት የለውም፡፡ መንግስት አላማውን ለማስፈፀም ወይም ለአገዛዝ እንዲመቸው መሰረታዊ ፍሬ ነገሮችን ያላከበረና መደበኛ የሕግ አወጣጥ ሥነ ስርዓትን የተከተለ ህግ ሊያወጣ ይችላል፡፡ ለምሳሌ የደቡብ አፍሪካው አፓርታይድ ስርዓት በህግ የተደገፈ ነበር፡፡ በሃገራችንም ፀረ ሽብር አዋጅ፣ የሲቪክ ማህበራት አዋጅ እና የምርጫ አዋጅ የገዥውን መንግስት ስልጣን ለማራዘም ሲባል የዜጎችን ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን የሚገድቡ በመሆናቸው መንግስት የህግ የባላይነትን በሚያስከብር መልኩ እያሻሻላቸው ይገኛል፡፡ በመሆኑም የህግ የበላይነት ሲባል በህግ አውጪው አካል መደበኛ የህግ አወጣጥ ስነ ስርዓትን ተከትሎ በወጣ ህግ መተዳደር ብቻ ሳይሆን ህጉ ባስገዳጅ ሁኔታ ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎችን ባከበረ መልኩ ስለመፅደቁ ትኩረት ይሻል ማለት ነው።

የህግ የባላይነት ፋይዳ እና አላባውያን

የሕግ የበላይነት የአስተዳደር መርህ ሲሆን ለሰላም ግንባታ፣ ለመልካም አስተዳደር፣ ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ልማት እንዲሁም ውጤታማና ተአማኒነት ያለው የፍትህ አስተዳደር ተቋማት ለመገንባት በመሰረታዊነት የሚወሰድ ፅንሰ ሃሳብ ነው፡፡ በዋነኛነት ግን ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮችን ለማሳካት የተወጠነ ሃሳብ ነው፡፡

እነሱም፡-

የመንግስትን የዘፈቀደ የስልጣን አጠቃቀምን ለመገደብ፣

የዜጎችን የንብረት፣ የነፃነት እና የሕይወት መብት በሌሎች እንዳይጣስ ጥበቃ ማድረግ ነው፡፡

በአንድ ሀገር መንግስት ውስጥ የህግ የበላይነት ስለመኖሩ ማረጋገጭ የሚሆኑ መገለጫ አላባውያን የተለያየ ቢሆንም በአለም አቀፍ ደረጃ የህግ የበላይነትን የሚያከብሩ ሃገራትን ደረጃ(rule of law index) የሚያወጣው ዓለም አቀፉ የፍትህ ፕሮጅክት(world justice project) የሚጠቀምባቸውን መለኪያዎች ከህገ መንግስታችን አኳያ የሚከተሉትን አምስት አላባውያን እናያለን፡፡

በህግ የተገደበ የመንግስት ስልጣ

ህጋዊነት

ገለልተኛና ነፃ የዳኝነት አካል

ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች መከበር

ሰላምና ደህነት

በሕግ የተገደበ የመንግስት ስልጣን

የመንግስት፣ የባለስልጣናቱና እንደራሴዎቹ ሥልጣን መገደብ ወይም መወሰን አለበት የሚለው የህግ የበላይነት መለኪያ መስፈርት ከሁለት ሺ ዓመት በፊት ጀምሮ ሲያቀነቅኑት የነበረ ሲሆን ዋና አላማውም መንግስት በዘፈቀደ ያለገደብ ልጓም እንደሌለው ፈረስ የሚፈነጭ ከሆነ የዜጎችን መብት በመጨፍለቅ ጨቋጭና አምባገነነ ይሆናል ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ መንግስት መጠቀም ያለበት የስልጣን መጠን የሃገርን እና የዜጎችን ሰላም፣ ደህንነት እና መብት አክብሮ ለማስከበር በሚያስችል መልኩ መሆን ይገባዋል፡፡ መንግስት በህግ የተሰጡትን ስልጣንና ተግባራት በሚፈፅምበት ወቅት በህግ በተቀመጡ አሰራሮች አግባብ መሆን ይገባዋል፡፡ ይህን ከተቃረነ በህግ ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፡፡ በተጨማሪም ህጉን ለመቀየር ወይም ለማሻሻል ፍላጎት ቢያድርባቸው ህግ የማውጣት ስልጣንን የሚገድቡ ወሰኖችን(constraints) በመጣስ ሊሆን አይገባም፡፡ የኢፌድሪ ህገ መንግስት በአንቀጽ 9 ማንኛም ህግ፣ ልማዳዊ አሰራር፣ የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከዚህ ህገ መንግስት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ከዚህ ድንጋጌ የምንረዳው ህግ አውጪው የሚያወጣው ህግ ወይም ሕግ አስፈፃሚው የሚወስነው ውሳኔ ወይም ህግ ተርጓሚው አካል ህግ ሲተረጉም ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎችን ማክበር እንዳለበት በስልጣናቸው ላይ ገደብ አስቀምጧል፡፡ ይህን ገደብ የጣሰ ህግ፣ ውሳኔ እና የህግ ትርጉም ተፈፃሚነት የለውም፡፡ የመንግስት አካላት በህግ በተሰጣቸው ስልጣን( separation of power) ብቻ እየሰሩ ስለመሆኑ ግልፅነትና ተያቂነት የሚያሰፍን የቁጥጥር ማድረጊያ መንገድ ሊኖር ይገባል፡፡ የኢፌድሪ ህገ መንግስት በአንቀጽ 12 ማንኛውም ሃላፊና የህዝብ ተመራጭ ሃላፊነቱን ሲያጓድል ተጠያቂ እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡ ቁጥጥርና ተጠያቂ ከሚደረግባቸው መንገዶች መካከል የሶስቱ የመንግሰት አካላት የእርስ በርስ ቁጥጥር መኖር( ለምሳሌ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 55(17-18) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስፈፃሚውን አካል የሚቆጣጠሩበትን አግባብ ደንግጓል) ፣ ለሲቨል ማህበራትና ለሚዲያ ተጠያቂ በመሆን፣ የመንግስት ስልጣን በህግ አግባብ ብቻ እንዲተላለፍ በማድረግ(ህገ መንግስት አንቀጽ 9(3) ይመለከቷል) ወ.ዘተረፈ ይገኝበታል፡፡

ህጋዊነት

የህግ የባላይነት ማረጋገጫ ከሚሆኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ የሕጋዊነት መርህ መኖር ሲሆን አንድ ህግ ከረቂቅ ጀምሮ ፀድቆ ተግባር ላይ በሚውልበት ወቅት ተደራሽ መሆኑ፣ ህጉ ግልፅና በቀላሉ የሚረዱት መሆኑ፣ ለውጥን የሚያስተናግድ፣ ተገማች የሆነ፣ ሊፈፀም የሚችል፣ በሁሉም ላይ በእኩል ተፈፃሚነት ያለው መሆኑ እና ማስፈፀሚ ስርዓትና ተቋም ሊኖር ይገባል የሚል ነው፡፡ አንድ የህግ ስርዓት እነዚህን መስፈርቶች የማያሟላ ከሆነ መንግስት እና ዜጎች ለህጉ ይገዛሉ ተብሎ አይጠበቀም፡፡ ይህ መርህ መከበሩ ዜጎች ባልወጣ ህግ እንዳይቀጡና የወጡትንም ህጎች አክብረው የእለተ ተለት ህይወታቸውን እንዲመሩ ይደረጋል፡፡ ህጉም ተገማች በመሆኑ ግብይት እንዲሳለጥ ይደርጋል፡፡ ምክንያቱም ትርፍና ኪሳራቸውን አስልተው እንዲገበያዩ ያስችላቸዋል፡፡ ለምሳሌ የውል ህግ በመኖሩ ዜጎች ያለ ስጋት በነፃነት እንዲገበያዮ ዋስትና ይሰጣቸዋል፤ ዉሉን ያላከበረ ተገዶ እንዲፈፅም ወይም ካሳ እንዲከፍል ስለሚደርግ ለሌላኛው ወገን ዋስትና ይሆናል፡፡ የንብረት ህግ ዜጎች ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን አውጥተው ያፈሩትን ንብረት በነፃነት እንዲጠቀሙ ጥበቃ ያደርጋል፡፡ የዚህ መርህ መስፈርቶች ህገ መንግስቱ ውስጥ ተደንግገው ይገኛሉ፡፡ ስለመንግስት አሰራር ግልፅነት እና ሁሉም ሰው በህግ ፊት እኩል መሆን በተመለከተ በሕገ መንግስቱን አንቀጽ 12(1) እና 25 እንደቅደም ተከተላቸው ተደንግገዋል፡፡

ገለልተኛና ነፃ የዳኝነት አካል

ነጻ የሆነ ፍ/ቤት የሕግ በላይነት መሰረታዊ ገፅታና ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መኖር ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ዋነኛው ባሕሪ ደግሞ የሰብዓዊ መብቶች መከበርና መረጋገጥ ነው፡፡ መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በሕገ-መንግስት ወይም በሌላ ሕግ መደንገጋቸው ብቻ በራሱ ለመብቶች መረጋገጥ ዋስትና ሊሆን አይችልም፡፡ እነዚህ መብቶች እውን ይሆኑ ዘንድ ነፃ ፍ/ቤት መኖር አለበት፡፡ ነፃነት የሌለው ፍ/ቤት የሰዎችን መሰረታዊ ሰብዓዊ መብቶች እንዲረጋገጥ ሊያደርግ አይችልም፡፡

በዜጎችና በመንግስት እንዲሁም በሰዎች መካከል ባሉ ግንኙነቶች ሳቢያ የሚነሱ የፍትሐብሔር ወይም ወንጀል ክርክሮችን ገለልተኛና ነፃ ሆኖ እልባት ሊሰጥ የሚችል ፍ/ቤት በሌለበት የሕግ በላይነት ሊረጋገጥ አይችልም፡፡ የሕግ በላይነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ደግሞ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እና መልካም አስተዳደር እውን ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ሰላምና ዘለቄታ ያለው ልማትም ዋስትና አይኖረውም፡፡ የዳኝነት ነፃነት ለኢንቨስትመንትና ለኢኮኖሚ እድገት መሰረት ነው፡፡ ባለሃብቱ በፍርድ ቤቶች ላይ እምነት እንዲኖረው በአንድ ሀገር ውሰጥ የዳኝነት ነፃነት መስፈንና መረጋገት ወሳኝ ነው፡፡ ስለዚህ ስለዳኝነት ነፃነት አስፈላጊነት ላይ ምንም ክርክር የለውም፡፡ የኢፌድሪ ህገ መንግስት በአንቀጽ 78 እና 79 ነፃ የዳኝነት አካል እንደተቋቋመ እና በየትኛውም ደረጃ የሚገኝ የዳኝነት አካል ከማንኛውም የመንግስት አካል፣ ከማንኛውም ባለስልጣን ሆነ ከማንኛውም ሌላ ተፅእኖ ነፃ መሆናቸው እና ዳኞች የዳኝነት ተግባራቸውን በሙሉ ነፃነት በህግ በመመራት እንደሚያከናውኑ ተደንግጓል፡፡ ጥያቄው ያለው የዳኝነት ነፃነት ስፋትና እና ተግባራዊ አፈፃፀሙ ላይ ነው፡፡

ሠላም፣ ስርዓትና ደህንነት

የአንድ ሃገር መንግስት፣ ህዝብና ነዋሪዎች ሰላም፣ ደህንነት፣ ሥርዓት መብትና ጥቅም መከበረ እና መረጋገጥ የህግ የባለይነት ዋነኛ ገፅታ ነው፡፡ ዘላቂ ዋስትና ያለው ሰላም ለማረጋገጥ የሚቻቻለው በአገራዊ ደህንነት፣ በመንግስትና በህዝብ ጥቅም፣ በግለሰቦች ደህንነትና መብት ላይ የሚፈፀሙ የወንጀል ድርጊት ዝግጅቶችንና ሴራዎችን አስቀድሞ ለመከላከል ሲቻልና ወንጀሎቹ ከተፈፀሙ አጥፊዎችን በህግ ስርዓት ተከታትሎ ለፍርድ ማቅረብና ለማስቀጣት ሲቻል ነው፡፡ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ፓለቲካ ድርጅቶች፣ የንግድ ድርጅቶች፣ ሌሎች ማህበራትና ማንኛውም ሰው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን በህገ መንግስቱና ሌሎች የህግ ማዕቀፎችና ድንጋጌዎች መሰረት በማድረግ የማከናውን የዳበረ ባህል ሲዳብሩ የምርጫ ውድድሮች ጨምሮ ሌሎች ኢኮኖሚያዊ፣ ፓለቲካውና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ህግና ሥርዓትን መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ መሆን ይገባቸዋል፡፡ መንግስት ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ ጉልበትን የመጠቀም(monopoly ofcoercive power) ብቸኛ መብት አለው፡፡ በመሆኑም ከህግ ከተፈቀደው ውጭ ዜጎች ወይም ሌሎች አካላት መብታቸውን ለማስከበር ሃይል የመጠቀም መብት የላቸውም፡፡ መንግሰት ሃገረ መንግስቱ የቆመበትን ሥርዓና ደህንነት ማስከበር አለበት ሲባል ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት የመከላከል ስራ መሰራት፣ ፓለቲካዊ ግጭቶችን(ሽብርተኝነት፣ አለመረጋጋትን፣ በታጠቁ ሃይሎች መካከል የሚደረግ ግጭትን) ውጤታማ በሆነ መልኩ መቀነስ እና የግል ችግርን ወይም በደልን ለመወጣት መደበኛውን የህግ ማስከበር ሥርዓት ከመከተል ይልቅ ሃይልን መጠቀም ማህበራዊ ተቀባይነት ያለው አድርጎ አለመፈፀም(ለምሳሌ የደቦ ፍትህ) በዋነኛነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ሰብዓዊ መብትና ነፃነቶች መከበር

ሰብዓዊ መብቶችና ነፃነቶች ከሰው ልጅ ተፈጥሮ የመነጩ የማጣሱና የማይገፈፉ ናቸው፡፡ ሃገራችን ህገ መንግስት የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች የሚከበሩ ስለመሆኑ በመሰረታዊ መርህነት የተደነገገ ከመሆኑም በላይ በማንኛውም ደረጃ የሚገኝ የፌደራል መንግስት የክልል ህግ አውጭ፣ አስፈፃሚና የዳኝነት አካል በህገ መንግስቱ ምዕራፍ ሶስት በተካተቱ የሰብዓዊ መብትና መሠረታዊ ነፃነቶች ድንጋጌዎች የማክበርና የማስከበር ሃላፊነትና ግዴታ ያለባቸው ስለመሆኑ በአንቀጽ 13(1) ተደንግጓል፡፡ መንግስት ሰብዓዊ መብቶችን የማክበርና የማስከበር ግዴታ የሚወጣው አስፈላጊውን የህግ፣ የአስተዳደርና ሌሎች እርምጃዎች በመዉሰድ ነው፡፡ መንግስት ከዜጎቹ ጋር ባለው የቀጥታ ግንኙነት እንዲሁም ዜጎች ባላቸው የእርስ በርስ ግንኙነት አንዱ የሌላውን መብት የማክበር ግዴታ አለበት፡፡ በመሆኑም የመንግስት ባለስልጣናትና ሰራተኞች ስልጣንና ሃላፊነታቸውን አላግባብና ከህግ ውጭ በመጠቀም የሚፈፀሙትን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድርጊቶችን እንዲሁም ሰዎች ባላቸው የጎንዮሽ ግንኙነት አንዱ የሌላውን መብትና ነፃነት የሚጥሱ ድርጊቶች የወንጀል ተጠያቂነትና ሃላፊነት የሚያስከትሉ ድርጊቶች መሆናቸውን በመደንገግ፣ በመከላከል እና ጥሰቱ ተፈፅሞ ሲገኝ በተሟላ ሁኔታ በወንጀል ፍትህ ስርዓቱ እንዲፈፀም በማድረግ መንግስት ሰብዓዊ መብት የማክበርና የማስከበር ግዴታውን በመወጣት የህግ የባለይነትን ማረጋገጥ አለበት፡፡

የሕግ የባለይነትን ለማረጋገጥ ምን ይደረግ ?

በአንድ ሃገር ውስጥ የህግ የበላይነት መኖር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው፡፡ በአንፃራዊነት ካልሆነ በስተቀረ ከላይ የተመለከቱት የህግ የበላይነት መገለጫዎች ሙሉ በሙሉ የተከበረበት ሃገር የለም፡፡ የህግ የበላይነት በጊዜ ሂደት የሚገነባ እና የጋራ ባሕል መገለጫ ይሆናል፡፡ መንግስት እና ዜጎች ሕጎች የእሴቶቻቸው መገለጫ እና ጥቅማቸውን ለማስከበር የወጡ መሆኑን ማመን አለባቸው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ህጎች በማክበርም ሆነ በማስከበር የራሳቸውን ድርሻ መወጣት ይገባቸዋል፡፡

Contact us via hihoney3@gmail.com

ማሰቃየትን ስለሚከለክሉ የኢትዮጵያ ህጎች

                                                        torture-report
በጢሞቲዎስ ዋርጎ
ክልል ዓቃቤ ህግ
የማሰቃየት ትርጉም
የተባበሩት መንግስታት በ1948 ማሰቃየትና ሌሎች ጭካኔ የተሞላባቸዉ ሰብአዊነት የጎደላቸዉ አዋራጅ ሆኑ አያያዞችንና ቅጣቶችን ለማስቀረት የተደረገ ስምምነት በአጭሩ «ማሰቃትን የሚከለክል ስምምነት» ተብሎ የሚጠራዉን የቃል ኪዳን ሰነድ አፅድቆ ስምምነቱም በበርካታ ሀገሮች ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያም በ1986 ዓ.ም የዚህ ስምምነት አባል ሀገር ሆናለች፡፡ ይህ ስምምነት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 9/4/ መሰረት የኢትዮጵያ ህጎች አካል ነዉ፡፡
ዓለም ዓቀፍ ማሰቃየትን የሚከለክለው የቃል ኪዳን ስምምነት በአንቀጽ 1 ንኡስ አንቀጽ 1 ላይ ማሰቃት ምን እንደሆነ በመግለጽ ይጀምራል፡፡ ይኸዉም ከራሱ ወይም ከሶስተኛ ወገን መረጃ ለማግኘት ወይም እንዲናዘዝ /እንዲለፈልፍ/ ለማድረግ በአንድ ሰዉ ላይ ሆን ብሎ የአካል ወይም የአእምሮ ስቃይ የሚያደርስ ድርጊት መፈጸም፤ እራሱ ወይም ሌላ ሶስተኛ ወገን ለፈጸመዉ ወይም ፈጽሟል ተብሎ በተጠረጠረበት ድርጊት ለማስፈራራት ወይም ለማስገደድ ወይም በማናቸዉም በልዩነት ላይ በተመሰረተ ሁኔታ የመንግስት ስልጣን ይዞ የሚሰራ ሰዉ ወይም በእርሱ ተነሳሽነት፣ስምምነት ወይም አዉቆ እንዳላወቀ በመምሰል በማሰቃት የሚፈጸም ማንኛዉም የማሰቃት ድርጊት ማሰቃየት ይባላል በማለት ይተረጉመዋል፡፡
ከዚህ ትርጉም አራት አበይት ጉዳዮች ተመልክተዋል፡፡ እነዚህንም እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡
የመጀመሪያዉ የድርጊቱን ዓላማ ይመለከታል፤ ይሀዉም ማሰቃት/ቶርቸር/ተብሎ የሚወሰደዉ ለስቃይ መነሻ የሆነዉ ድርጊት ወይም ስቃዩ እንዲደርስ የተደረገበት ዓላማ ስቃይ ከሚደርስበት ወይም ከተፈፀመበት ሰዉ ከራሱ ወይም ከሌላ ሶስተኛ ወገን መረጃ ለማግኘት ወይም ይህ ሰዉ እንዲናዘዝ ተብሎ ሲፈፀም ነዉ፡፡ ይህ ማለት በሰዉ ላይ ስቃይ ሊፈጥሩ የሚችሉ ነገሮች ሁሉ ማሰቃየት/ቶርቸር/ አይሆኑም፡፡ ስቃይ የፈጠሩት ድርጊቶች ከተሰቃዩ ወይም ከሌላ ሶስተኛ ሰዉ አስገድዶ መረጃ ለማግኘት ተብሎ የሚደረጉ መሆን አለባቸዉ፡፡ ለምሳሌ አንድ መርማሪ ፖሊስ አንድን ተመርማሪ የተጠረጠረበት ድርጊት በተመለከተ ሲመረምር እዉነቱን አዉጣ በማለት ከደበደበዉ ማሰቃት ተፈጸመ ማለት ነዉ፡፡
ሁለተኛዉ ስቃዩን የሚያደርሱ ድርጊቶች በተሰቃዩ ላይ የሚያደርሱትን የስቃይ ዓይነት ይመለከታል፤ ስቃይ የሚያደርሱ ድርጊቶችና ማሰቃት የሚባሉት የሚያደርሱት የስቃይ ዓይነት አካላዊ ወይም አእምሮአዊ ሊሆን ይችላል፡፡ አካላዊ ስቃይ የሚባለዉ በተሰቃዩ ላይ ቀጥተኛ የሆነ የአካል ጉዳት ሲደርስበት ነዉ፡፡ አእምሮአዊ የሚባለዉ ተሰቃዩ ቀጥተኛ የሆነ የአካል ጉዳት ባይደርስበትም በተፈጸሙበት ደርጊቶች ምክንያት የአእምሮ ወይም የስነልቦና ጉዳት ሲደርስበት ነዉ፡፡ ለምሳሌ፤ ፖሊስ አንድን ተመርማሪ የተጠረጠረበት ድርጊት ሲመረምር እዉነቱን እስከሚያወጣ ድረስ በማለት የተመርማሪዉን ቤተሰብ ቢያስርበት ይህ ሁኔታ በተመርማሪዉ ላይ ስነልቦናዊ ጉዳት ያደርሳል፡፡
ሶስተኛዉ በተሰቃዩ ላይ የሚፈጸሙት ድርጊቶች የሚከናወንበት መንገድ ይመለከታል፤ ይኸዉም አካላዊ ወይም አእምሮአዊ ስቃይ በማስፈራራት፣በማስገደድ ወይም ሌላ ዓይነት ድርጊት በማድረስ ሊፈፀም ይችላል፡፡ ስቃይ ፈፃሚዉ ራሱ በቀጥታ ድርጊቱን ባይፈጸምም ሌሎች ሲፈጸሙ አይቶ እንዳላየ ቢመስል ድርጊቱን እንደፈጸመ ይቆጠራል፡፡ለምሳሌ፤ መርማሪ ፖሊስ ተመርማሪዉን ቢደበድበዉ፣ሲደበድበዉ እንደሚያድር ቢገልጽለት፣ እዉነቱን ካልተናገረ ከባድ የሆነ የእስር ቅጣት እንደሚደርስበት ወይም ከልጆቹ አንዱ ላይ የአካል ጉዳት እንደሚደርስባቸዉ ቢገልጽለት ወዘተ በእነዚህ መንገዶች ማሰቃት ተፈፅሟል ማለት ነዉ፡፡
አራተኛዉ ከፈጻሚዉ አኳያ ይታያል፤ የማሰቃት ድርጊት ተፈጸመ የሚባለዉ ማሰቃትን የፈጸሙት በዋናነት የመንግስትን ስልጣን የያዙ አካላት ሲሆኑ ነዉ፡፡ለምሳሌ የድርጊቱ ፈጻሚ መርማሪ ፖሊስ ሲሆን ፖሊስ ደግሞ የመንግስት አካል በመሆኑ የተፈጸመዉ ድርጊት የማሰቃየት ተግባር ነዉ ማለት ነዉ፡፡
ማሰቃየትን የሚከለክሉ የኢትዮጵያ ህጎች
ሀ) ኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 9(4) እና አንቀጽ 13(2) ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎች የሀገሪቱ ህጎች አካል መሆናቸውን ይደነግጋሉ፡፡ እነዚህ አንቀጾች ማሰቃየትን የሚከለክለው ስምምነት የሀገር ውስጥ ህግ ሆኖ ተፈጻሚነት እንዲያገኝ የሚያስችሉ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ህገመንግስቱ ራሱ ማሰቃየትን ይከለክላል፡፡
ማሰቃየትን የሚመለከተው የህግ መንግስቱ ክፍል አንቀጽ 18 ሲሆን ይህ አንቀጽ ማንኛውም ሰው ጭካኔ ከተሞላበት ኢ-ሰብአዊ ከሆነ ወይም ክብሩን ከሚያዋርዱ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት እንዳለው ይደነግጋል፡፡
ህገ መንግስቱ ማሰቃየትን/ቶርቸርን/በግልጽ አይጠቅስም፡፡ ነገር ግን አንቀጽ 18 ላይ የተከለከሉት ድርጊቶች ስንመለከት ባጠቃላይ ማንኛውም ጭካኔ የተሞላባቸውና ኢሠብአዊ ድርጊቶችን የሚከለክል በመሆኑ ማሰቃየትን/ ቶርቸርን/ የመሰለ ኢ-ሰብአዊና ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት የሚከለክል ለመሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡
ለ) የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕግ
በ1954 ዓ/ም የወጣው የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ሕግ አንቀጽ 31 ፖሊስ በምርመራ ወቅት በተመርማሪው ላይ ማድረግ የሌለበትን ድርጊቶች ይዘረዝራል፡፡ የማሰቃየትን ትርጉም ቀደም ብለን ስንመለከት ማሰቃየት ከሚፈጸምባቸው ሁኔታዎች አንዱ ድርጊቱን የሚፈጽመው ሰው ስቃዩ ከሚደርስበት ሰው ላይ መረጃ ለማግኘት ሲል የሚያደርገው እንደሆነ ተገልጾአል፡፡ ከነዚህም ሁኔታዎች አንዱ ፖሊስ ተጠርጣሪን በሚመረምርበት ወይም በሚጠይቅበት ወቅት ነው፡፡ የፖሊስ የምርመራ ተግባር በህግ ካልተገዛና ገደብ ካልተደረገበት ተመርማሪውን ግለሰብ ለስቃይ ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ ይህንንም ግምት ውስጥ በማስገባት ይመስላል የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕግ አንቀጽ 31(1) ፖሊስ የተመርማሪውን ቃል ሲቀበል ተመርማሪውን መደለል ወይም እንዲደልል ማድረግ፣ የማስፈራራት ወይም የሀይል ስራ ወይም ሌሎች ከሕግ ውጪ ያለ ዘዴዎች መፈጸም ወይም ማድረግ አይችልም በማለት የሚደነግገው፡፡ምንም እንኳን ድንጋጌው ማሰቃየት ወይም ቶርቸርን በግልጽ ባይጠቅስም ማሰቃየት አሰቃቂ የሆነ የሀይል ድርጊት በመሆኑ ፖሊስ ምርመራ በሚያካሄድበት ወቅት ይህንን ድርጊት መፈጸም እንደሌለበት ህጉ በግልጽ ይደነግጋል፡፡ ማሰቃየት ወይም በአንቀጽ 31(1) የተዘረዘሩትን ማናቸውንም ድርጊት በመፈጸም የተገኘ ማስረጃ በህግ ፊት ተቀባይነት የለውም
ሐ/ የወንጀል ሕግ
በ1996 ዓ/ም ተሻሽሎ የወጣው የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 424 የማስፈራራት ወይም ከሰብአዊ ርህራሄ ውጪ ወይም ለሰው ልጅ ክብር ተቃራኒ የሆነ ድርጊት የፈጸመ በተለይም ድብደባ፣የመንፈስ ስቃይ፣የጭካኔ ተግባር ያደረሰ የመንግስት ሰራተኛ በእስራት ወይም በመቀጫ እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ አንቀጹ ሰፋ ያለ ሁኔታዎችን የሚያካትት ሲሆን በነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ማሰቃየት/ቶርቸር/ የሚካተት መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ይህ አንቀጽ የወንጀል አድራጊውን ብቻ ሳይሆን ለወንጀል መፈጸም ተጠያቂ የሆነውን ትእዛዝ የሰጠውን ባለስልጣን ጭምር የሚቀጣ ነው፡፡ በትእዛዝ ሰጪው ባለስልጣን ላይ የተጣለው ቅጣት ከፈጻሚው ቅጣት ከበድ ያለ መሆኑንም መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ቶርቸር የፈጸመ ማንኛውም ባለስልጣን ከተጠያቂነት የማያመልጥ መሆኑንም ህጉ በሚገባ ያስገነዝባል፡፡
ማሰቃየትን የሚከለክሉ ህጎችን ከማስፈጸም አኳያ የዓቃቤ ህግ ሚና
ሀ) ህጎችን የማስተማር ግዴታ
ማሰቃየትን ለማስወገድ በቶርቸር ስምምነት በአንቀፅ 10 ከተመለከቱት እርምጃዎች መካከል ማሠቃየትን በተመለከተ ትምህርት እና ስልጠና መስጠት አንዱ ነው፡፡ ማሠቃየትን በዋናነት ማስቀረት የሚቻለው ድርጊቱ እንዳይፈፀም በመከላከል ነው፡፡ ይህንን ለማድረግ ደግሞ ማሠቃየትን ሊፈፀሙ ይችላሉ ተብለው የሚገመቱ ሰዎችን ለይቶ ማሠቃየት አስከፊ፣ አሰቃቂና ኢ-ሠብአዊ ድርጊት መሆኑን እና ይህም ማስተማር የተከለከለና የተኮነነ ድርጊት መሆኑን በግልፅና በቅድሚያ ማሳወቅ ነው፡፡ ይህንን ማድረግ ባለማወቅ ማሠቃየትን ሊፈፅሙ የሚችሉ ሰዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ለማድረግ ይጠቅማል፡፡ ከዚህም አልፎ ማሠቃየትን በተመለከተ በቂ እውቀት እንዲሰራጭና ድርጊቱን በአንድነት ለመኮነንና ለመከላከል ይቻላል፡፡ ስለዚህ ዓቃቢያነ ህግ ስቃይን የሚከለክለው ስምምነት ይዘት በየደረጃዉ ላሉት የህብረተሰብ አካላት በአጠቃላይ እንዲሁም በስራ አጋጣሚ የማሰቃየት ተግባር ለመፈጸም ተጋላጫ ለሆኑ የመንግስት አካላትን በተላይ በተለያየ ዘዴዎች ትምህርትና ሥልጠና በመስጠት የድርጊቱን የመከላከል ሀላፊነትና ግዴታ አለባቸው፡፡
ለ) የወንጀል ምርመራ የመምራት እና ህጋዊነቱን የማረጋገጥ ግዴታ

በወንጀል ተጠርጥረዉ ተይዘው ወይም ታስረው የሚገኙ ግለሰቦች የሚደረግላቸው አያያዝ፣ የምርመራ ዘዴዎችን ወዘተ… ማሰቃየትን ከማስወገድ አኳያ በየጊዜው የዓቃቤ ህግን ጥብቅ ክትትል የሚፈለግ ነዉ፡፡ በ2003 ዓ.ም የወጣዉ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ፍትህ ፖሊሲ የወንጀል ምርመራ የመምራት ሀላፊነት የዓቃቤ ህግ እንደሆነ ሀገራዊ የፖሊሲ አቅጣጫ ያስቀምጣል፡፡በመሆኑም ዓቃቢያነ ህግ በተጠርጣሪዎች ላይ የሚደረገዉን የወንጀል ምርመራ በመምራት ብሎም በተመርማሪዉ ላይ የሚደረገዉን ምርመራ ዓለም አቀፍ የቶርቸር ስምምነት መለኪያዎችን የሚያሟሉ ህጋዊ ሂደቶችን የተከተለ ስለመሆኑ የማረጋገጥ ሀላፊነት አለባቸዉ፡፡
ሐ/ የግለሰብን አቤቱታ የማስተናገድ እና ምርመራ የማከናወን ግዴታ

ማንኛውም ግለሰብ ማሠቃየት ተፈፅሞብኛል ብሎ አቤቱታ ሲያቀርብ ዓቃቢያነ ህግ አቤቱታ ተቀብሎ ራሱ ወይም ከመርማር ፖሊስ ጋር በመሆን በአፋጣኝ የመመርመር ግዴታ አለበት፡፡ ከዚህም በተጨማሪ አቤቱታ ያቀረበው ግለሰብ እና ምስክሮቹ የማጉላላትና የማስፈራራት ድርጊቶች እንዳይፈፀምባቸው ተገቢዉ የህግ ጥበቃ ሊደረግላቸዉ ይገባል፡፡
በሌላ በኩል ዓቃቢያነ ህግ በሚሰሯቸዉ አከባቢ/በግዛት ክልላቸው/ ውስጥ በወንጀል ተጠርጥረዉ ምርመራ በሚደረግባቸዉ ተጠርጣሪዎች ማሰቃት/ቶርቸር/ተፈፅሟል ብለው ሲጠረጥር ወይም ሲያምን አስፈላጊው የማጣራትና የመመርመር እርምጃ እንዲደረግ የማድረግ ሀላፊነት እና ግዴታ አለባቸዉ፡፡ ይህ እርምጃ አፋጣኝና ከአድልዎ ነፃ መሆን አለበት፡፡

ሃተታ ዘ ካራማራ!

ሃተታ ዘ ካራማራ!
በኃይለማርያም ይርጋ
(ኢትዮጵያ ትቅደም!)
መንጌና ዝያድ ባሬ ራሳቸውን ማርክሲስት ሌሊኒስት ብለው የሰየሙ (self proclaimed) የሶቨየት ህብረት ጥገኛ ሃገር ሃገር (satellite state) መሪዎች ነበሩ። እንደውም ኢትዮጵያን፣ ደቡብ የመንን፣ ጅቡቲንና ሶማሌን ያቀፈ ማርክስሲስት ሌሊኒስት ኮንፌድሬሽን እንዲመሰርቱ ሃሳብ  ቀርቦ መንጌ ፈቃደኛ ሲሆን ዛይድ ባሬ ባለመስማማቱ ሳይሳካ ቀረ። ዝያድ  የታጠቀውን የራሽያና አሜሪካ ሰራሽ ዘመናዊ መሳሪያ ተማምኖ አዋሽ ድረስ ይዘልቃል ድንበሬ ብሎ ወረራ ጀመረ።

ትጥቅ አልባው መንጌ….

መንጌ የታጠቀው አብዛኛው ከጣልያን ጦርነት የተረፈ ሞይዘር፣ አልቤንና ምንሽር ነበር። ጀነራል አማን አምዶም (የኔ ጀግና) ከኪሲንጀር ጋር በጓዳዌ ስሜት(ሁለቱም የኮሪያ ዘማች ናቸዋ!)  ደብደቤ ተፃፅፎ ኮንግረሱ ቀጥታ የመሳሪያ ድጋፍ የሚከለክል ህግ ቢያወጣም እንደምንም በዱቤ የመቶ ሚሊየን ዶላር ጦር መሳሪያ ፈቀዱለት። ይህ መሳሪያ መሳሪያ መርከብ ላይ ተጭኖ ጉዞ ሊጀምር ሲል መንጌ ጀነራሉን ጨምሮ እነዛን የሃገር ባለውለታዎች ላይ  አብዮታዊ እርምጃ ወሰድኩ ብሎ አወጀ😭…ሰብዓዊ መብት ተቀዳሚ የወጭ ጉዳይ ፓሊሲው የነበረው የፕሬዝዳንት ከርተር አስተዳደር ጦር መሳሪያውን ከመርከብ ላይ አራግፎ፣ አስቀረው።

የኛ ሰዎችም የገዛነውን መሳሪያ ከለከሉን ብለው አስወሩ። አሁንም ብዙ ሰው እምነቱ ይኸው ነው።

መንጌም በግልፅ የሶቭየት ጎራ መቀላቅሉን በይፋ አወጀ። ወደ ሶቭየት በሮ ቤርዜኔቭ ጋር በሸናና ብሎ ፅዋውን አጋጭቶ ጨለጠ። ፍላጎቱን ጠየቁት፣ የሚፈልገውን የመሳሪያ አይነት ዘርዝሮ እሳወቁ። ይሁን አሉ።

አሜሪካኖች ይባስ ብለው በቀጠናው የሃይል ሚዛኑ (power balance) ለመጠበቅ  በተዘዋዋሪ ዝያድ ባሬን ደገፉ። ለምን ? ሌላ ጊዜ።  የሆኖ ሆኖ  ዘመናዊ መሳሪያ አልነበረም ሳይሆን ከጥላትህ ጋር አቻ የሚያደርግህ ጥራትና ብዛት ያለው መሳሪያ አልነበረም። አሜሪካ የሰለጠኑ ምርጥ መኮንኖች ነበሩት።  መንጌ ስልጣኑን ጠቅሎ አልያዘም ነበር፣ ሽግግር ላይ ስለነበር በውስጥ ጉዳይ ተወጥሮ ነበር።

ሶቨየት ስለምን ረዳችን?

በዚህ ወቅት ሶቨየት ህብረት ከሁለት አንዱን መምረጥ ነበረባት። ከርዕዮተ ዓለም ይልቅ አካባቢያዊ ጥቅም(strategic interest) የሚያስከብርልኝ የቱ ነው ብላ ገምግማ  በህዝብ ብዛት በአስር እጥፍ የምትበልጠውንና በቀይ ባህር አቋርጦ የሚያልፈውን የነዳጅ ጫኝ መርከብ ለመቆጣጠር የሚያስችላትን ምቹ መልክአምድር ያላት ኢትዮጵያን መረጠች፣ መንጌንም አይዞህ አለሁልህ አለችው ይለናል ክርስቶፎር አንድሪው  The World Was Going Our Way: The KGB and the Battle for the Third World በተሰኘው መፅሃፉ። ቀይባህር እንዲህ ጠቅሞን ነበር😢 አባይና የጣና ሃይቅም ጆኦፓለቲካዊ ፋይዳውም ቀላል አልነበረም።  አሁን ያለን የህዝብ ብዛት ወሳኝ አቅማችን( hard power) እንደሆን ልብ ይሏል፣ ሸማች ነዋ። 

ዝግጅት በመንጌ በኩል..

መንጌ ይርጋ ዱባለን፣ ጥሌን እና ሜሪ አርሚዴን ይዞ “የፍየል ወጠጤ”፣ “እኔስ ለሃገሬ” እያስጨፈረ ህዝቡን ከጫፍ ጫፍ አነቃንቆ ከሶስመቶ ሺ በላይ ሚሊሻና መደበኛ ወታደር አሰለጠነ፣ ግን ወቅቱ የሚጠይቀውን ዘመናዊ መሳሪያ አልያዘም ነበር። አንዳንድ ፊልሞችን አይታችሁ እንደሆን ሰልጣኞች ከጣውላ የተሰራ ጠመንጃ መሳይ ይዘው ልምምድ ሲያደርጉ የነበረው። ምን ተሻለ? ሶቨየት ህብረት ከላይ እንደገለፅኩት ከጥቅሟ አንፃር  ኩባንና ምስራቅ ጀርመን አስተባብራ በነፍስ ደረሰችልን።

ተዓምራዊው ርብርብ..

ለሶስት ወር ያህል የራሽያ የጦር አውሮፕላኖች መሳሪያ ጭነው #በየሃያ ደቂቃው የኢትዮጵያን መሬት ይረግጡ ነበር፣ ይለናል ክርስቶፎር አንድሪው ከላይ በተገለፀው መፅሃፉ ።  225 አውሮፕላኖች በማጓጓዙ ሂደት ተሳትፈዋል። 17,000 የኩባ ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አንድ ሺ የሚሆኑ የራሽያ የጦር አማካሪዎች ጋር እንዲቀላቀሉ ተደርጓል። 400 በመረጃ ደህንነት እና የጦር ምህንድስና የሰለጠኑ የምስራቅ  ጀርመን ወታደሮችም በረው ደርሰዋል።

ወደ ፍልሚያው

እንደ ዝያድ ባሬ መሳሪያ ቢታጠቁት ምን ይበጃል ከሃገር ፍቅር ስሜት እና ውኔ የተሞላ የመዋጋት ፍላጎ (The will to fight)  ከሌለው፣ ኢትዮጵያኖች ግን በዚህ አይታሙም። ሁሉም በሚችለው ተረባረበ። የአሪሲ እናቶች ከቀን ተሌት ገብስ ቆልተውና ፈጭተው በቅቤ ያበደ  አስራ አራት ኢነትሬ ከነተሳቢ ጭቆ አዘጋጅተው እንዳቀረቡ ከአንድ ጋዜጠኛ ሰምቻለሁ። ዛይድ ባሬ በመጣበት ድባቅ ተመትቶ በዚች እለት በካራማራ ተሰናበተ። ይህ ድል ሁሉም የኢትዮጵያ የፓለቲካ ሃይሎች ተሳትፈውበታል በተለይም መኢሶን ድርሻው ትልቅ ነበር። ኢሕአፓ ይታማል። ድሉ ግን የሁሉም ነበር!

የፍየል ወጠጤ ልቡ ያበጠበት፣
እንዋጋ ብሎ ለነብር ላከበት
..

ለ… ውዲቷ ለእናት ኢትዮጵያ

ታጥቄ

ጠንክሬ

የምሰዋላት ነኝ እኔስ ለሃገሬ

ጠ… ላቶቹዋን እቃወማለሁ

አጥብቄ

በብርቱ

ስለ ሀገር ፍቅር ገባኝ በእውነቱ
Eyob Dechasa  Nebyou Surafel ጓዶች እንኳን አደረሳችሁ!

Successful

When you think of the word “successful,” who’s the first person that comes to mind and why?

Elon mask is the first person that comes in my mind when i think of the word successful. Because his origin is Africa. How on earth the person who comes from Africa to america become the number one billioner in the world unless America is the land of apportunity.

ለማይቀረው እድል ፈንታችን እንዘጋጅ

የወትሮ ዝግጁነት…

እጩ መኮንን እያለሁ ለወታደራዊ መስክ ልምምድ ወደ በረሃ ሄደን ደኮንን፡፡ በስለጠናው የመጀመሪያ ቀን በቃል ገለፃ ከተደረገልን መመሪያዎች መካከል ጠላት መቼ፣ እንዴት እና በየት በኩል ሊመጣ እንደሚችል እርግጠኛ ሆነን ማወቅ ስለማንችል ምንጊዜም የወትሮ ዝግጁነት ያስፈልጋችኋል የሚል ነው፡፡ የወትሮ ዝግጁነት ማለት ክላሽህን አፅድተህና ፈትሸህ፣ ጋደም ብትል እንኳ በግማሽ ልብ፣ ጫማህንና ፋቲግህን ሳታወልቅ፣ ድንኳንህን ገርበብ አድርገህ መተኛት አለብህ፡፡ የንቅናቄ ተኩስ ቢሰማ መንዘላዘል የለብህም፣ ዘለህ እስከ ሙሉ ትጥቅ ምሽግ ውስጥ መግባት እና እንዳመጣጡ ምላሽ መስጠ፡፡ ከልሆነ፣ ተበላህ፡፡

ዓለም አሁን ያለችበት ሁናቴ የማትገመት፣ ሥርዓቷ የእንቧይ ካብና ውስብስብ ሆኑዋል ይለናል የሙኒክ የፀጥታና ደህንነት የጥናት ውጤት፡፡ በመሆኑም እንደ ወታደር በወትሮ ዝግጁነት መጠበቅ እንደሚገባ ለአባል ሃገራቱ የመፍትሄ ሃሳብ ያቀርባል፡፡

የሙኒክ የፀጥታ ኮንፈረንስ…..

የሙኒክ የደህንነትና የፀጥታ ኮንፈረንስ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚዘጋጁ የኢኮኖሚና የፓለቲካና ስብሰባዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀስ ነው፣ ደህንነት እና ፀጥታ የማናቸውም ነገር ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ፡፡ በመሆኑም የኮንፈረንሱን ውጤት ኢንቨስተር ባለሃብቶች፣ መንግስታትና እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ይጠብቁታል፡፡ ውጤቱን ዓለም ያለችበትን ሁኔታ በግልፅ የሚያስቀምጥ በመሆኑ ከዚሁ አንፃር እቅዳቸውን ይገመግማሉ፣ ያሻሽላሉ፣ አስፈላጊ ከሆነም ሰርዘው አዲስ ተስማሚ እቅድ ያቀዳሉ፡፡

በዘንድሮው (2023) ኮንፈረንስ የዓለም የንግድ ትስስር፣ የልማት ትብብር፣ የንግድ መሰረተ ልማቶች፣ የኢነርጂ አቅርቦት እና የሰብዓ መብት ሁኔታ በጥናት ተለይቶ ቀርቧል፡፡ በጥናቱ መሰረት ሃገራት ከንግድ ትስስር (Interdependence) ይልቅ ጥገኝነትን አጥብቦ ራስን ለመቻል ጥረት በማድግ የደህንነት ተጋላጭነታቸውን ለመቀነስ እየሰሩ ይገኛል፡፡ የንግድ መሰረተ ልማቶች ለነፃ ንግድ እንቅስቃሴ የዘረጉዋቸውን ህግጋትና ሁኔታዎችን (WTO rules and regulations) ሆን ብሎ በመተላለፍ የሃገር ውስጥ ኩባንያዎቻቸው ላይ ትኩረትና ማበረታቻ እየሰጡ ይገኛል፡፡ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችንም እንዲሁ እንደ ብሄራዊ የተፅዕኖ መሳሪያነት በመጠቀም ሌሎች ሃገሮች ላይ ጥቅማቸውን ለማስከበር ተፅዕኖ ለማሳረፍ እየተጠቀሙባቸው ይገኛል፡፡ ከዚህ አንፃር አንፃር አሜሪካና ቻይና ከዓለም የነፃ ገበያ ሥርዓት እንዴት ራሳቸውን እያገለሉ እንደሆነ ማየቱ ከሃገራችን አንፃር ምልከታችንን ስለሚያሰፋልን ለማየት እንሞክራለን፡፡

አሜሪካና ቻይና ከሥርዓቱ ማፈግፈግ….

አሜሪካ ከዓለም ነፃ ገበያ መውጣት የጀመረቸው በትራምፕ ዘመን ነበር፡፡ ትራምፕ የዓለም አቀፉን የንግድ ድርጅት ህጎች በመተላለፍ ቻይና ወደ አሜሪካ የምትልካቸው ሸቀጦች ላይ ከፍተኛ ታሪፍ በመጣል ጀመረ፡፡ ከዚያም የቴሌኮሙኒኬሽን መሰረተ ልማት አቅራቢ የሆነውን ሕዋዌ ከአሜሪካ ምድር በማዕቀብ አባረረው፡፡ ቻይናም ባቅሟ ተናዳ አኩሬ አተር ከአሜሪካ አላስገባም አለች፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ጆ ባይደን ደግሞ ከትራምፕ የበለጠ ፓፕሊስት ሆኖ መጣ፡፡ አረንጓዴ ኢነርጂ ሽግግር የሚል እቅድ ይፋ አደረገ፡፡ ይህ እቅድ በሂደት አሜሪካን ከዓለም የንግድ ስርዓት በማስወጣት ሃገር ውስጥ ሽግግር አድርጎ እንደገና ወደ አለም መመለስ የሚል ነው፡፡ ይህን ለማሳለተጥ የዋጋ ግሽበት ማስተካከያ(Inflation Reduction Act) በማውጣት የአውሮፓን ካምፓኒዎችን ከውድድር ውጭ የሚያደርግ መድሎ በመፈፀም የገንዘብ ድጎማ ለአሜሪካ ካምፓኒዎች አደረገ፣ በተለይ ለኤሌክትሪክ መኪና አምራች ኩባንያዎች፡፡ የኤሎን ማስኩ ቴስላ ቢሊያን ዶላር አፈሰ፡፡ የፈረንሳይ ፕሬዝዳን ማክሮን እሳት ጎርሶ ነጩ ቤተ መንግስት ተገኘ፡፡ የዓለም የንግድ ድርጅት ሕግን የሚጣረስ በመድሎ የተሞላ፣ ውድድርን የማያበረታታ የገንዘብ ማበረታቻ መስጠት አይገባም ብሎ ሞገተ ፣ ወፍ የለም፡፡ ለፈረንሳይ ይህ ሁለተኛ በደለሏ ነበር፣ ከአውስትራሊያ ጋር የገባቸውን የኑክሌር ሰብማሪን መርከብ ውል አሜሪካና እንግሊዝ በአሻጥር እንዲፈርስ አድርገውባት ነበር፡፡ ወደ ጆ እንመለስ…የአርብ ነዳጅ ዘይት በቃኝ ብሎ የገልፍ ባህረ ሰላጤትነት ትቶ ወደ ሃገሩ ገባ፣ ወደ ሃገሩ ሲገባ ባዶ እጁን አልነበረም በባህረ ሳላጤው ቅኝት እያደረገ የመርከቦችን የአንቅስቃሴ ደህንነት ሲጠብቅ የነበረው የባህር ሃይሉን ጠቅልሎ ነበር የውጣው፡፡ የች ወሳኝ ጉዳይ ነች፣ እንዳትረሳ፡፡ ከዚያም ቻይና በባሎን ሰለለችኝ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ አለ፡፡ አንዷ ተተኳሽ አራት መቶ ሺ ዶላር በሚያወጣ ሚሳይል ባሎኒን አጋየው፡፡ በዚህ ጉዳይ የሪፐብሊካኖችና አሜሪካኖች አንድ መሆን ይገርማል፣ የጋራ አላማቸው እንደሆነ ትረዳለህ፡፡ አፈ ጉባኤ ናንሲ ፓሊሲን ታይዋን ላካት፣ ቻይና አበደች፣ ወታደራዊ ትዕይንት አሳየች፣ አንዣበበች፡፡ ጆ ያልተጠበቀ ውሳኔ አሳለፈ፣ ለቻይና ማናቸውንም ሴሚኮንዳክተር መሸጥ እንደማይቻል ፣ ቻይና ውስጥ በዚህ ሙያ ዘርፍ እየሰራ ያለ ማናቸውም አሜሪካው ስራዉን ወይም ዜግነቱን ይምረጥ አለ፡፡ የቺፕስ ጦርነት ይሏል! ጎን ለጎን ደግሞ በአሜሪካ ክልሎች እና በሜክሲኮ የኢንዱሰትሪ ፓርክ እየሰሩ ቻይና ውስጥ የነበሩ ፋብሪካዎቻቸውን ቀስ በቀስ ማስወጣት ጀመሩ፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን አውሮፓም ገበያ እያጣ እየተበደለ መሆኑን እንዳትረሳ፡፡

ወደ ቻይና እንደሂድ…..

ቻይና የአሜሪካ አካሄድን ተረድታ ታምርት (made in china 2025) የሚል እቅድ ነድፋ እየሰራች ይገኛል፡፡ የዚህ እቅድ አላማ የንግድ ጥገኝነት የደህንነት ስጋት ስለፈጠረብን ማናቸውንም ነገር ሃገራችን ውስጥ እያመረትን፣ እየሸጥን፣ እየሸመት ተጋላጭነት በመቀነስ ሸማችን መሰረት ያደረገ የንግድ እንቅስቃሴ (consumption led economy) ሊኖረን ይገባል የሚል ነው፣ ዋቃ ይሁናት:: የሚሳካ አይመስለኝም፣ 70 በመቶ የምግብ፣ የግበርና ግብዓትና የኢነርጂ ጥገኛ ነችና፡፡ ዝርዝሩን ሌላ ጊዜ፡፡ ይህን ህልሟን እውን ለማድረግ እንደ አሜሪካ የዓለም የንግድ ድርጅት ህግን መተላለፍ ጀመረች፣ ኢንዱስትሪዎቿን በመደጎምና መድሎ በመፈፀም አውሮፓን ከገበያዋ ማስወጣት፡፡ የምግብ ምርቷን ለመጨመር የአፍሪካ ገበሬዎችን ከገበያ በሚያስወጣ መልኩ ድጎማ አደረገች፡፡ አውስትራሊያና ሉትኒያ ላይ የንግድ ማዕቀብ በመጣል እንዲሁ ሕግ ተላለፈች፡፡ ራሽያን በቃል እና በንግድ ግንኙነት ደገፈች፡፡ ሳይቤሪያ በኩል የጋዝ ጥማቷትን ከራሽያ በመውሰድ አረካች፡፡ አውሮፓዎች ተደናደዱ፣ አውሮፓ ስልህ ጀርመን እያልክ አንብብ፡፡ ቻይና ከአውሮፓ ጋር ያላት የንግድ ግንኙነት ከራሽያ ጋር ካላት ጋር ስለሚበልጥ በሂደት ስለጦርነቱ ለራሽያ ያላትን ውግንና እየተወች መጣች፡፡ የሆኖ ሆኖ፣ ይህ ቻይና ታምርትና ትሸምት እቀድ የቻይና ገበያን አውሮፓውያን እንዳይጠቀሙ የሚያደርግ ነው፡፡

መልካም እድል ለኛ….

የአሜሪካምና የቻይና የኢኮኖሚ ፓሊሲ አውሮፓን ገበያ የሚያሳጣ ነው፡፡ የአውሮፓ ኢኮኖሚ ደግሞ የውጭ ንግድ መራሽ (export led economy) ስለዚህ አማራጭ የገበያ መዳረሻ ይፈልጋሉ፡፡ መዳረሻቸው ደግሞ አፍሪካ ነው፡፡ ከአፍሪካ ደግሞ ሰብሰሃራን አፍሪካ፡፡ ከሰብሰሃራ አፍሪካ ደግሞ የአምስት ሃገራትን ድንበር የምታዋስነው ከመቶ ሃያ ሚሊየን በላይ ሕዝብ ያላት The power house of Africa እየተባለች የምትጠራው ወጣቷ፣ ያንተው ኢትዮጵያ ነች፡፡ እንደ ታዋቂው የጂኦፓለቲካ ሊቁ ፒተር ዛሂን ትንበያ ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ ቀድሞ የገባ አውሮፓ ሃገር አትራፊ እንደሚሆን ይገልፃል፡፡ ለዚህም ይመስላል ጀርመን እየተንደረደረች ያለቸው፡፡ ከውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሃላፊዋ እስከ መራሂተ መንግስቱ ወደ ሃገራችን መጥቷል፡፡ መምጣት ብቻ ሳይሆን የልማት፣ የደህንነትና መከላከያ ትብብር ስምምነት አድርገናል፡፡ ይህ አልበቃ ብሎ ኢትዮጵያ ኢንቨስት ለሚያደርጉ ኩባንያዎች የኢንሹራንስ መድህን መዋጮ በክፈል አባል አደረገችችን፣ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን በ21 ሚሊዮን ዩሮ በመደገፍ ሃገራችን ሰላምና የተረጋጋች፣ የንብረት ባላቤትነት ነፃነት እና የሕግ የበላይነት የሰፈነባት ለኢንቨስትመንት ተመራጭና ምቹ የሆነች ሃገር እንድትሆን እየሰሩ ይገኛል፡፡

ከኛ ምን ይጠበቃል…..

የወትሮ ዝግጁነት!

ይህን የአለም ነባራዊ ሁኔታ መረዳትና ዝግጁ መሆን፡፡ ዝግጁ የምንሆነው ልዩነትን በሰጥቶ መቀበል ለማጥበብ በቅንነት መወያየት፣ በአንድ ሃገር ልጅነት አንተ ትብስ እኔብስ ወደ እድል እጣፈንታችን ለመድረስ መተባበር፡፡ መተባበር፡፡ መተባበር፡፡

ይህን ትብብር ለማሳጣት፣ ልዩነታችን በልዩነት ሸንተሮቻችን መጠን ሊያሰፉ የሚፈልጉ በሃገራችን ላይ ጥቅም ያላቸው ታሪካዊም ሆነ እርስ በርስ በሚደረግ ፍትጊያ ሊያባሉ የሚፈልጉ ሃይሎች እንዳሉ ማወቅ ይገባል፡፡ ትጥቀ ያነገበው እንዳይፈታ ለሃገሩ እና ለብሄሩ እየተጋለ እየመሰለው የሃገሩን ዘላቂ ጥቅም ወደ ጎን አድርጎ በተራዘመ የርስ በርስ ግጭት ውስጥ እንደንቆይ እና ይህ ታሪካዊ አካጋጣሚ እንዲያልፈን እና የነሲ ሸቀጥ ማረገፊያ ሊያደርጉን ይችላሉ፡፡ ይህን ጉዳይ ለመፍታት ሕዝባችን ዋነኛ መሳሪያ ሊሆን ይገባል፡፡ ሕዝቡን ከፊታችን ስላለው ታሪካዊ እጣ ፈንታው እናሳውቀው፣ እናንቃው፣ ጥቅሙን ይረዳ፡፡ ይህን ከተረዳ ከእድል ፋንታዊ ሊያደናቅፉት የሚችሉትን አይታገሳቸውም፡፡ ሰላሙንና ደህንነቱን በወትሮ ዝግጁነት ራሱ ይጠብቃል፡፡

የወትሮ ዝጅነት!

የትራምፕ የክስ ቻርጅ

ፕሬዝዳንቱ በኒወርክ ክልላዊ መንግስት ዓቃቤ ህግ  በኩል በአንድ መዝገብ 34 ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ የክሱ ዋና መነሻ ምክንያት የንግድ የሂሳብ መዝገብ ላይ ሀሰተኛ ሰነድ አያይዘዋል የሚል ነው፡፡ ሀሰተኛ ሰነድ ያያዙት ደግሞ ለማጭበርበር እና ሌሌ ወንጀል ለመፈፀም ወይም ለመደበቅ ወይም ለማገዝ ሆን ብለው የፈፀሙት እንደሆን ይገልፃል፡፡ 34ቱም ክሶች አንድ ዓላማ ለማሳካት  በተለያየ ወቅት የተፈፀሙ ድርጊቶች ቢሆንም ለእያንዳንዱ ድርጊት ለብቻው ክስ ቀርቦበታል፡፡ ከሀገራችን የወንጀል ህግ እና ክስ አመሰራረት አንፃር እንዴት ያዩታል?